channel logo
Gizat S1

“ግዛት” የተሰኘ ልብ አንጠልጣይ ቴሌኖቬላ በዲኤስቲቪ-አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካቾች መቅረብ ሊጀምር ነው

ዜና
28 ማርች 2025
ጋዜጣዊ መግለጫ
Gizat S1

አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵ   ከኢትዮጵያውያን ዕውቅ የፊልም ባለሙያዎች ጋር በድንቅ ጥምረት ስራዎችን እያቀረበ የሚገኘው አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካቾች እጅግ አስደሳችና ለደንበኞች የሚመጥኑ አዳዲስ ይዘቶችን በብዛት እያደረስ ነው፡፡ ላለፉት ዓመታት ግዙፍ፣ አዳዲስና እውቅ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማዎች ታሪክ ፋና ወጊ የሚያድርጉትን ተወዳጅና እለታዊ የሆኑ ተከታታይ ቴሌኖቬላዎችን ማቅረቡና እያቀረበ መሆኑም ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ አነጋጋሪ፣ ልብ አንጠልጣይና በላቀ ጥራትና ሙያዊ ብስለት የተዘጋጀውን “ግዛት” የተሰኘ አዲስ ቴሌኖቬላ ለተመልካቾች ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

“ግዛት” ቴሌኖቬላ The Queenከተሰኘው የኤምኔት ተወዳጅ የደቡብ አፍሪካ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ታሪክ በመነሳት የኢትዮጵያን ወግ፣ ባህል፣ እሴትና የአኗኗር ይትባሃል በጠበቀ ሁኔታ የተዘጋጀ ድራማ ነው፡፡ “ግዛት”በታዋቂ የፊልም ባለሙያ ደን ታቸው ፕሮዲዩስ የተደረገ ሲሆን በቴሌቪዥን ድራማዎች ትወና አንቱታን ያተረፉ ድንቅ ተዋንያን ተሳትፈውበታል። ከእነዚህም መካከል ታምሩ ብርሃኑ፣ ቢኒያም ወርቁ እና ሜሮን እንግዳ ይገኙበታል።  “ግዛት” ሌሎች በማራኪ ትወናቸው ገፀ-ባህሪያትን ሆነው የሚተውኑበትና በአቦል ቴሌቪዥን ለረጅም ጊዜያት በየዕለቱ ከሰኞ እስከ አርብ የሚተላለፍ ቴሌኖቬላ ነው፡፡

ግዛት ልብ እያንጠለጠለ የሁለት ቤተሰቦችን የግዛት ሽኩቻ፣ የገንዘብ ፍቅርና ጥቅም ፍለጋ ብሎም በተለያየ አጋጣሚ በሚፈጠሩ ክስተቶች የቤተሰብ ፍቅር በገንዘብ ሲፈተን የሚያሳይ ሲሆን በየክፍሉ `ቀጥሎ ምን ሊፈጠር ነው` በሚያስብሉ ድርጊቶች የተሞላ ድንቅ ተከታታይ ድራማ ነው።

“ግዛት” የሀረግ ገፀ-ባህሪን ተላብሳ የምትጫወተው ሜሮን እንግዳ ሙሉ ጊዜዋን ድራማ በማዋል ገፀ-ባህሪዋን ልዩ ውበትና ጉልበት በመስጠት የትወና ብቃ ያሳየችበት ሲሆን በሌላ በኩል ታምራት በለጠ ወይም ሰመረ ደግሞ አዲስ ችሎታና ብቃት ለፊልም ኢንዱስትሪው ይዞ የመጣበት ነው። ይህ ተዋናይ ለድራማው እንዲተውን እጩ የሆኖ የቀረበው የቀረፃ ወይም የፕሮዳክሽን አባል ሆኖ እያሰራ ባለበት ወቅት የግዛት ዳይሬክተር ኤደን ጌታቸው እምቅ ችሎታውን ተገንዝባ `ሰመረ`ን ወክሎ እንዲጫወት መርጣዋለች።

የመልቲቾይስ ኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ገሊላ ገ/ሚካኤል “መልቲቾይስ/ዲኤስቲቪ ለሀገር በቀል ይዘቶች መጎልበት ግንባር ቀደም አካል እንደመሆ መጠን በገር ውስጥ መዝናኛዎች ለደንበኞቻችን ምርጥ ምርጡን እያቀረበ ነው። ተመልካቾቻችንን የሚማርኩና ከዕለተ ዕለት ህይወታቸው ጋር ቀረቤታ ያላቸውን ታሪኮችን በላቀ ጥራት ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ አሁን ደግሞ የፕሮዳክሽን ቡድ አባላትም ሆኑ የአቦል ቴሌቪዥን ተመልካቾች አስደሳችና ልዩ የመዝናኛ ጊዜን “ግዛት” እለታዊና ተከታታይ  ቴሌኖቬላ እንደሚያጣጥሙ እምነታችን የጸና ነው’ ብለዋል፡፡

“ግዛት” ሰኞ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በጎጆ ፓኬጅ ዲኤስቲቪ-አቦል ቻናል 465 ከምሽቱ 2:30 መተላለፍ የሚጀምር ሲሆን ተመልካቾች ሊያመልጣቸው የማይገባ ድንቅ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ መሆኑም ተገልል፡፡


ይህንን እና ሌሎችም ተጨማሪ አዝናኝ ሃገርኛ ድራማዎችን በዲኤስቲቪ-አቦል ቻናል በጎጆ ፓኬጅ እንዲከታተሉ ዲኤስቲቪ ያስገቡ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!